ሐምሌ ፲፫
(ከሐምሌ 13 የተዛወረ)
ሐምሌ ፲፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፲፫ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፶፫ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ዮሐንስ፤ ማቴዎስ፤ እና ማርቆስ ደግሞ ፶፪ ቀናት ይቀራሉ።
አቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች ለማስተካከል
- ፲፱፻፴፯ ዓ/ም -የዩናይትድ ስቴትስ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዓለም ባንክን (The World Bank) እና ዓለም አቀፍ ገንዘባዊ ዕድርን (International Monetary Fund - IMF) የመሠረተውን የብሬቶን ዉድስ (Bretton Woods Agreement) ስምምነት አፀደቀ
- ፲፱፻፵፫ ዓ/ም - የዮርዳኖስ ንጉሥ፣ ቀዳማዊ አብዱላ ኢየሩሳሌም ላይ በሚገኝ መስጊድ ውስጥ የዓርብ ጸሎት ላይ እንዳሉ በአንድ የፍልስጥኤም ተወላጅ እጅ ተገደሉ።
- ፲፱፻፷፩ ዓ/ም -አፖሎ 11 የተባለው የጠፈር መንኮራኲር ጨረቃ ላይ ሲያርፍ የሰላሳ ስምንት ዓመቱ ኒል አርምስትሮንግ የጨረቃን ነጠፍ በመርገጥ የመጀመሪያው የሰው ልጅ ሆነ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በቆጵሮስ ደሴት ላይ በተካሄደ መፈንቅለ መንግሥት የአገሪቱ ፕሬዚደንት ሊቀ ጳጳስ ማካሪዮስ ከስልጣን በወረዱ በአምስተኛው ቀን፣ የቱርክ ሠራዊቶች ደሴቷን ወረሩ። እስካሁንም ይቺ ደሴት ለሁለት ተከፍላ የግሪክ ቆጵሮስ እና የቱርክ ቆፕሮስ በመባል የሁለቱ ዘሮች የልዩነት መተዳደሪያ ደሴት ናት።
- ፲፱፻፸፪ ዓ/ም -የተባበሩት መንግሥታት ድርጀት አካል የሆነው የጸጥታ ምክር ቤት አባላት ድርጅቱ ኢየሩሳሌምን የእስራኤል ዋና ከተማነቷን እንዳይቀበሉ በሙሉ ድምጽ ወሰነ።
ልደት ለማስተካከል
ዕለተ ሞት ለማስተካከል
ዋቢ ምንጮች ለማስተካከል
- (እንግሊዝኛ) http://en.wikipedia.org/wiki/July 20
🔥 Top keywords: ዋናው ገጽፋይዳ መታወቂያልዩ:Searchውክፔዲያ ውይይት:ምንጭጌየአድዋ ጦርነትጥላሁን ገሠሠጂፕሲዎችአፈወርቅ ተክሌሥርዓተ ነጥቦችኢትዮጵያአማርኛሀጫሉሁንዴሳየአክሱም ሐውልትውይይት:ዋናው ገጽአበበ ቢቂላሚላኖላሊበላጀጎል ግንብኢትዮ ቴሌኮምኤችአይቪመጽሐፍ ቅዱስቅዱስ ያሬድአክሱምዓፄ ቴዎድሮስቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕትዳግማዊ ምኒልክአርሰናል የእግር ኳስ ክለብአውሮፓገብረ ክርስቶስ ደስታ ግጥሞችማርያምሆሣዕና በዓልጉግል2ኛው ዓለማዊ ጦርነትየኦሎምፒክ ጨዋታዎችt8cq6ዘጠኙ ቅዱሳንየቅርጫት ኳስየጋብቻ ሥነ-ስርዓትእርዳታ:ይዞታ